ሐምሌ 2/2018
ኢትዮጵያ የሰው ሰራሽ አስተውሎትን ከመጠቀም ባለፈ በዘርፉ አለም አቀፍ የምርምር ስራንም እየሰራች ነው ተባለ፡፡
በአለም አቀፍ ህትመቶች ላይ የቀረቡ ከ60 በላይ ጥናቶች እስካሁን መሰራታቸው ተነግሯል፡፡
ይህን የተናገረው የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ነው።
እነዚህ ጥናትና ምርምሮች በሳይንሱና በአካዳሚው አለም ከፍተኛ የምርምር እውቀና እና ማረጋገጫ አግኝተው በአለም አቀፍ ጆርናሎች እየታተሙ ነውም ተብሏል።
በሌላ በኩል የኢትዮጵያ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ስነ-ምግባራዊ የሰው ሰራሽ አስተውሎት መርህን የተከተለ እንደሆነም ኢንስቲትዩቱ ተናግሯል።
Comments