ጥቅምት 19፣2017
በየጊዜው በሚከሰቱ ማንነትን መሠረት ያደረጉ የታጠቁ ቡድኖች ጥቃቶች፤ በመንግሥት እና በታጠቁ ቡድኖች መካከል በሚደረጉ ግጭቶች እና ዘላቂ ፖለቲካዊ እና አስተዳደራዊ መፍትሔ ባልተሰጠባቸው የወሰን ይገባኛል ጥያቄዎች ምክንያት በሚከሰት ግጭት እና ጦርነት ሰዎችን ከመኖሪያ ቀያቸው ማፈናቀላቸውን ቀጠለዋል ሲል ኢሰመኮ ተናገረ፡፡
በአፋር፣ አማራ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ጋምቤላ፣ ሐረሪ፣ ኦሮሚያ፣ ትግራይ፣ ሶማሊ፣ ደቡብ ኢትዮጵያ እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልሎች ተፈናቅለው እርዳታ ጠባቂ የሆኑ በየመጠለያ ጣቢያው እና ከማኅበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው የሚኖሩ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች አንዳሉ ኮሚሽወጣው ሪፖርት አስረድቷል።
Comments