TRACK
በምህንድስናው ዘርፍ የሰለጠኑ ወጣቶች ጀርመንኛ ቋንቋ ሰልጥነው በጀርመን ሀገር በሙያቸው የሚሰሩበት እድል መመቻቸቱ ተናገረ
የካቲት 14 2017
በምህንድስናው ዘርፍ የሰለጠኑ ወጣቶች ጀርመንኛ ቋንቋ ሰልጥነው በጀርመን ሀገር በሙያቸው የሚሰሩበት እድል መመቻቸቱ ተናገረ፡፡
ከዩኒቨርስቲ ምሩቃን ባለፈ በኮንስትራክሽን ዘርፍ በቴክኒክና ሙያ የሰለጠነም የእድሉ ተጠቃሚ ይሆናል ተብሏል፡፡
እድሉን አግኝቶ በጀርመን የስራ ላይ ስልጠና የሚጀምር ኢትዮጵያዊ መነሻ የወር ደሞዝ 1 ሺህ 80 ዩሮ ይሆናል ተብሏል፡፡
በየአመቱ ደመወዙ እንደሚጨምር እና ተገቢው ኢንሹራንስም አንደሚገባለት ተነግሯል፡፡
የጀርመን ኮንስትራክሽን ፌዴሬሽን በኢትዮጵያ ይፋ ያደረገው አዲስ ፕሮጄክት አንዱ አላማም ይኸው መሆኑን ሰምተናል ፡፡
Comments