ሰኔ 20፣ 2016
የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ለ40/60 እና ለ20/80 ቤት ገንብቶ ለነዋሪዎቹ ለማድረስ ችግር ገጥሞኛል አለ፡፡
መንግስት አቅሙ ላላቸው መሬት እያቀረበ በማህበር ተደራጅተው ቤት እንዲገነቡ እያደረገ ነው ሲል ኮርፖሬሽኑ ተናግሯል፡፡
ይሁንና ይህ አቅሙ ላላቸው ብቻ እንጂ ሌሎችን ቆጣቢዎች አያካትትም ተብሏል፡፡
በአዲስ አበባ ለረጅም ዓመታት ቤት ለማግኘት የቆጠቡ ነዋሪዎች እኛ ቤት ሳናገኝ በኛ ገንዘብ መንግስት ለሌሎች ቤት ሰርቶ እየሰጠ ነው ይላሉ፡፡
ኮርፖሬሽኑ በበኩሉ በእነሱ ገንዘብ ሳይሆን በመንግስት አቅም የተገነቡ ቤቶችን ለልማት ተነሺዎች እንደተሰጠ ተናግሯል፡፡
Comments