ግንቦት 28 2017   የገበያቅኝት - የእንቁላል ዋጋ መናር
TRACK

ግንቦት 28 2017 የገበያቅኝት - የእንቁላል ዋጋ መናር

Avatar

የእንቁላል ዋጋ ከሶስት ወራት በፊት ከነበረው በእጥፍ ጨምሯል፡፡

በዘርፉ ተሰማርተው የነበሩ የእንቁላል አምራቾች ከስራው በብዛት መውጣታቸውንም ሰምተናል፡፡

ለዋጋው መወደድ ዋንኛው ምክንያት የምርት እጥረት ነው፤እጥረቱም የመጣው በርካታ የዶሮ አርቢዎች በኪሳራ ከስራው በመውጣታቸው እንደሆነ የዶሮ አምራቾችና አቀናባሪዎች ማህበር ነግሮናል፡፡

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ የሚታይበትን የእንቁላል ዋጋን በከተማዋ ባሉ ከሾላ ገበያ ጀምሮ በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች ተዘዋውረን ጠይቀናል፡፡

በቅኝታችን በጀሞ፣ቄራ፣ፒያሳና ሾላ አካባቢ ያሉ ገበያዎችን ተመልክተናል፡፡

በዚህም መሰረት በጀሞና ቲያሳ አካባቢ አንድ እንቁላል የሃበሻው እስከ 23 ብር የፈረንጁ እስከ 21 ብር ይሸጣል፤በቄራ ገበያ አከፋፋዮች የሃበሻውን እንቁላል 21ብር፣የፈረንጁን 20 ብር እየሸጡ ነው፡፡

በሾላ ገበያ ግን የተወሰነ የዋጋ መቀነስ እንዳለ ተመልክተናል፡፡ በዚህ ገበያ ሁለቱም አይነት እንቁላል በ20 ብር ይሸጣል፡፡

ያነጋገርናቸው ነጋዴዎችም የእንቁላል ዋጋ ከወትሮው በተለየ ዋጋው እንዲጨምር ምክንያቱ የምርት እጥረት ነው፤ከገበያው የሚፈልገው ያህል መጠን እየቀረበ አይደለም ይላሉ፡፡

በዚህም ምክንያት አንዳንድ ነጋዴዎች ከገበያው እየወጡ መሆኑንም ነግረውናል፡፡

Comments

Avatar