የካቲት 9/2018
በቅርቡ ብሔራዊ ባንክ በውጭ ምንዛሪ መመሪያ ላይ በ19 ጉዳዮች ላይ ማሻሻያዎች ካደረገባቸው ጉዳዮች መካከል የፎርዋርድ የውጭ ምንዛሪ ግብይት ያለ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ማረጋገጫ ማካሄድ እንዲችሉ መፍቀዱ ነው፡፡
ይህ ማለት አንድ ነጋዴ አንድ ሺህ ዶላር የሚያወጣ ሰሊጥ ወደ አረብ ሀገር ቢልክ ከባንኮች ጋር የላከው ሰሊጥ ገበያ ላይ ተሽጦ የሚመጣው የውጪ ምንዛሪ ከወዲሁ ባንኩ የሚገዛበትን ዋጋ መዋዋል ይችላል፡፡
ይህ ሲያደርግ ውል የተስማሙበት ጊዜ እና ሰሊጡ የተሸጠበት ወቅት ያለው የውጪ ምንዛሪ ዋጋ ከፍና ዝቅ ማለት የሚፈጥረውን ስጋት ከወዲሁ ለማስቀረት ይረዳል ተብሏል፡፡
አቶ ጥላሁን ግርማ የፋይናንስ ኢኮኖሚ እና የኢንቨስትመንት አማካሪ ናቸው፡፡ የፎርዋርድ የውጪ ምንዛሪ ግብይት በፅሁፍ የተፈቀደ ነገር እስካሁን አልተመለከትሁም ይላሉ፡፡
Comments