የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ፡፡
TRACK

የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ፡፡

Avatar

ጥቅምት 20 2018

የሚሰጣቸውን ምክረ ሃሳቦች ያለ በቂ ምክንያት የማይፈፅሙ ተቋማት በህግ እንዲጠየቁ ለማድረግ ቢሞክርም ባለው የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ፡፡

ተቋሙ የአስተዳደር በደል ደረሰብን እምባችን ይታበስልን የሚሉ አቤት ባዮችን ቅሬታ በመቀበልና በማጣራት እንዲሁም አስተዳደራዊ በደሎች መፈፀማቸውን ሲያረጋግጥ ማስተካከያ እንዲደረግ ለተቋማት ምክረ ሃሳቦችን ይሰጣል፡፡

ቅሬታ የቀረበባቸው ተቋማት አሰራሩ እንደሚፈቅደው በ1ወር ጊዜ ውስጥ ምክረ ሃሳቡን መፈፀማቸውን ወይም አለመፈፀማቸውን ከእነምክንያቱ ለእምባ ጠባቂ ተቋም ማሳወቅ እንዳለባቸው የተቋሙ ምክትል እምባ ጠባቂ የኔነህ ስመኝ (ዶ/ር )ነግረውናል።

ምክረ ሃሳቡን ተቀብለው ማስተካከያ የሚያደርጉ ተቋማት እንዳሉ ሁሉ ያለ በቂ ምክንያት ለአቤት ባዮች ቅሬታ ምላሽ የማይሰጡ ተቋማት በህግ እንዲጠየቁ እንደሚደረግ የሚያነሱት ሃላፊው ይሁንና የእምባ ጠባቂ ተቋምን ምክረ ሃሳብ ያለመፈፀም ወንጀል በመሆኑ ለአቃቢ ህግ ክስ እንዲመሰረት ብንልክም ጉዳዩን እንደ ሌላ ወንጀል እንዲጣራ ወደ መርማሪ ፖሊስ የሚልኩት በመሆኑ ስራችን ላይ እንቅፋት እየፈጠረ ነው ሲሉ ያስረዳሉ፡፡

Comments

Avatar