በኢትዮጵያ በጨርቃ ጨርቅ እና አልባሳት ኢንዱስትሪ ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች፤ የሚደርስባቸው የመብት ጥሰት ቀጥሏል ተብሏል፡፡
ይህ የተባለው ፎረም ፎር ሶሻል ስተዲስ (Forum For Social Studies) የተሰኘ ተቋም በጨርቃ ጨርቅ እና አልባሳት ኢንዱስትሪ ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞችን በተመለከተ እየሰራው ላለው ፕሮጀክት ከሚመለከታቸው አካላት ግብዓት ለመሰብሰብ ባዘጋጀው መድረክ ላይ ነው፡፡
የፕሮጅክቱ ከዋኝ ብድን አባል የሆኑት ደግነት አበባው(ዶ/ር) በጨርቃ ጨርቅ እና አልባሳት ኢንዱስትሪዎች ተቀጥረው የሚሰሩ ሰራተኞች የበዙ ችግሮች እየገጠሟቸው እንደሆነ አንስተዋል፡፡
Comments
ኢትዮጵያውያን ንግግር ስታደርጉ በአማርኛ ብቻ ይሁን እንግሊዝኛ መቀላቀል አዋቂ አያሰኝም ቋንቋችንን ጠበቅ::