በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቄያቸው ምስራቅ ወለጋ ጉብሰዮ ወረዳ የተመለሱ ከ141 በላይ አባዎራዎች ድጋፍ ስለተቋረጠባቸው መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡
TRACK

በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቄያቸው ምስራቅ ወለጋ ጉብሰዮ ወረዳ የተመለሱ ከ141 በላይ አባዎራዎች ድጋፍ ስለተቋረጠባቸው መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡

00:00

ታህሳስ 6 2018

በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቄያቸው ምስራቅ ወለጋ ጉብሰዮ ወረዳ የተመለሱ ከ141 በላይ አባዎራዎች ድጋፍ ስለተቋረጠባቸው መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡

የአካባቢው ቡሣ ጎኖፋ ወይም የእርዳታ ማስተባበሪያ በበኩሉ ድጋፍ እንዲቀጥል ለሚመለከተው የበላይ አካል ባሳውቅም ድጋፍ ግን ሊቀጥል አልቻለም ብሏል፡፡

በምስራቅ ወለጋ ጉቡሰዮ ያሉ ተፈናቂዎች የካቲት 11 ቀን 20015 ዓ.ም በአካባቢው አንፃራዊ ሰላም በመፈጠሩ ተጠልለው ከሚገኙበት የደብረብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቀያቸው የተመለሱ ናቸው፡፡

አሁን ላይ ወቅቱን ያለጠበቀ ድጋፍ ከግብረ ሰናይ ድርጅቶች ከሚቀርብላቸው ውጪ እንደቀድሞ ምንም አይነት ድጋፍ እንደማይቀርብላቸውም ተናግረዋል፡፡

Comments

00:00