ነሐሴ 22፣2016
በአዲሰ አበባ የጋብቻ ፣ የልደት፣ የሞት የመሳሰሉ ሁነቶች የሚመዘገቡበት እና መረጃ የሚሰጥበት የመረጃ አያያዝ በአዲስ ሊተካ ነው፡፡
አዲሱ ስርዓት የአገልግሎት መቋረጥን ያስቀራል፣ ተገልጋዩም በቤቱ ሆኖ ጭምር አገልገሎቱን እንዲያገኝ ያስችላል ተብሏል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ከዚህ ቀደም የነበረው የመረጃ አያያዝ ስረዓት ከተማውን የማይመጥን ሆኖ በመገኘቱ በአዲስ ልቀይረው ነው ብሏል፡፡
ኤጀንሲው አሁን እየተጠቀመበት ያለው የመረጃ አያያዝ እና አሰጣጥ ስረዓት የዛሬ 10 ዓመት የለማ መሆኑንም ተናግሯል፡፡
Comments