በሰሜኑ ኢትዮጵያ ከሁለት ዓመታት በፊት የተካሄደውን የርስ በርስ ጦርነት ተከትሎ በአለም ባንክና በኢትዮጵያ መንግስት ስምምነት መሰረት በሶስተኛ ወገንነት የተመረጠው የመንግስታቱ ድርጅት ተቋም(UNOPS) ለሽሬው ስሁል ሆስፒታል ለጤና መርጃ መሳሪያዎች ግዥ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የድጋፍ ስምምነት ማድረጉ ተሰማ፡፡
የአፍሪካ ህብረት ወኪል እንዲሁም መቀመጫቸውን አዲስ አበባ በማድረግ የአካባቢ ሀገራትን በበላይነት የሚመሩት የተባበሩት መንግስታት የፕሮጀክት ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ወርቅነሽ መኮንን ከጣሊያን ኤምባሲ ጋር ስለተደረገው ስምምነት ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ነግረዋል፡፡
Comments