ህዳር 10 2018
‘’አዲስ ወደ ስራ ለሚገቡ ኢንተርፕራይዞች ብድር የሚሰጡ የፋይናንስ ተቋማት እጅግ ዝቅተኛ ናቸው’’ ሲል የኢንተርፕራይዝ ልማት ኢንስቲትዩት ተናገረ፡፡
በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ ውስጥ የኢንተርፕራይዞች ቁጥር በሚፈለገው ልክ እንዳያድግና ዘርፉ ለውጥ እንዳያመጣ አድርጓል ተብሏል፡፡
የኢንተር ፕርነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሀሰን ሁሴን(ዶ/ር) እንደ አፍሪካ እንኳን ቢታይ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የኢንተርፕራይዞች ቁጥር እጅግ አነስተኛ ነው ይላሉ፡፡
ለዚህ ብዙ ምክንያቶች ቢኖርም ዋነኞቹ መንግስት በሚፈለገው ልክ አስቻይ ሁኔታ አለመዘርጋቱ ፣ ሀሳብ ያላቸው ወጣቶች ወደ ስራ ለመግባት ድፍረት ማጣት ተጠቃሽ ናቸው ይላሉ፡፡
ከዚህ ባለፈም ሀሳባቸውን ወደ ስራ ለማስገባት የሚጥሩ ስራ ፈጣሪዎች የፋይናንስ አቅርቦት እጥረት ይገጥማቸዋል ይህ ትልቁ ችግር ነው ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ ወደ ስራ ሊለወጥ የሚችል ሀሳብ ላለው ሰው ብድር መስጠት ወይም የአይዲያ ፋይናንሲንግ ህግ መፅደቁ የሚታወስ ሲሆን ይህ ህጉ እስካሁን ስራ ላይ ሲተገበር እየተመለከቱ አለመሆኑን ሀሰን ሁሴን(ዶ/ር) ጠቅሰዋል፡፡
Comments