መስከረም 7 2018
የተማሪዎች ጫማ እና ቦርሣ ፕሮጀክት የቆዳ ኢንዱስትሪውን ልማት እንዲደግፍ በሚል ነው በ2013 የተጀመረው።
በሀገር ውስጥ ባለሃብቶች የተያዙ አነስተኛ እና መካከለኛ የቆዳ ኢንዱስትሪዎች የሚያመርቷቸውን ጫማና ቦርሳዎች፤ ክልሎች ገዝተው ለተማሪዎች እንዲያቀርቡ ታስቦ የተቀረጸ ፕሮጀክት ነው።
በአንድ በኩል ለሀገር ውስጥ የቆዳ ፋብሪካዎች የገበያ ዕድል የመፍጠር ዓላማ ያለው ሲሆን በሌላ በኩል ፤ ተማሪዎች ልክ እንደ ደንብ ልብስ ሁሉ የሚያስፈልጓቸው ጫማና ቦርሳ እንዲሟሉላቸው የማድረግ ግብ ይዟል።
ወጣቶች የሀገር ውስጥ ምርትን መጠቀም እንዲለማመዱ ታስቦ የተጀመረም ነው።
መጀመሪያ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በኋላ ላይ ደግሞ ኦሮሚያ ፤ ሲዳማ እና ሃረሪ ክልሎች ለምርቶቹ ፍላጎት ማሳየታቸውን ተከትሎ ፕሮጀክቱ አገር አቀፍ እንዲሆን ተወስኗል፡፡
ፕሮጀክቱ 2013 ላይ ይፋ ሲሆን ሰፊ የማስተዋወቅ ስራ እንደተሰራ ያስታወሱት የቆዳ ኢንዱስትሪ ምርምር እና ፤ልማት ማዕከል ስራ አስኪያጅ አቶ ዙልፍካር አባጅሐድ ለተወሰኑ ተማሪዎች በመንግስት በጀት ጫማ ተገዝቶ መቅረቡንም ተናግረዋል።
ተማሪዎች የሀገር ውስጥ ምርትን መጠቀም በስፋት ከተለማመዱ በኋላ ምርቶቹን እየገዙ የማቅረቡን ሃላፊነት ወላጆች እንዲረከቡ የማድረግ ውጥን ተይዞ እንደነበር የሚያስታውሱት አቶ ዙልፍካር የተወሰኑ ስራዎች መሰራታቸውንም ነግረውናል።
ለፕሮጀክቱ የህግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት ፤ ማህበረሰቡ ስራውን እንዲረከብ ማድረግ እና ተገቢውን በጀት መመደብ ላይ ግን ክልሎች እንዳሰብነው አልሆኑልንም ብለዋል አቶ ዙልፍካር።
Comments