በአማራ ክልል በአንዳንድ አካባቢዎች በቀጠለ የሰላም እጦት ምክንያት የትምህርት ሥርዓቱ ጫና ውስጥ ወድቋል፡፡
TRACK

በአማራ ክልል በአንዳንድ አካባቢዎች በቀጠለ የሰላም እጦት ምክንያት የትምህርት ሥርዓቱ ጫና ውስጥ ወድቋል፡፡

Avatar

የካቲት 9/2018

በሰሜኑ ጦርነት እና አሁንም በአማራ ክልል በአንዳንድ አካባቢዎች በቀጠለ የሰላም እጦት ምክንያት የትምህርት ሥርዓቱ ጫና ውስጥ ወድቋል፡፡

ባለፉት አራት እና አምስት አመታት በክልሉ በነበሩ፣ አሁንም ድረስ በቀጠሉ ሰላም እጦቶች እና በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉ ችግሮች ምክንያት ዘርፉ በብዙ ውጣ ውረድ እያለፈ ነው ያለው የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ለዚህም ድጋፍ እሻለሁ ብሏል፡፡

በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት ከ4 ሺህ ትምህርት ቤቶች በላይ ጉዳት የደረሰበት የክልሉ ትምህርት ቢሮ ከነበረበት ችግር ሳያገግም አሁንም ድረስ በቀጠለው የሰላም እጦት ምክንያት ትምህርት ቤቶች ጉዳት እየደረሰባቸው እንደሆነ ነግሮናል፡፡

በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ ጉዳት የደረሰባቸው ትምህርት ቤቶች እንዳሉ ያነሱት የትምህርት ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ጌታቸው ቢያዝን ጉዳቱ ምን ያህል ነው የሚለው ግን ጥናት ያስፈልገዋል ብለዋል፡፡

Comments

Avatar