ህዳር 11 2018
ለኢትዮጵያ ሁለተኛ የሆነው የዓይን ባንክ በጅማ ተከፍቶ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ተነገረ፡፡
የኢትዮጵያ ደምና ህብረ ህዋስ ባንክ እንደተናገረው በአዲስ አበባ ዳግማዊ ምኒሊክ ሆስፒታል ውስጥ ካለው የአይን ባንክ በተጨማሪ ለረጅም ጊዜ ተይዞ በነበረ ዕቅድ በክልል ከተማ የዓይን ብሌን የሚሰበሰብበት ባንክ ተከፍቷል ብሏል፡፡
የኢትዮጵያ ደምና ህብረ ህዋስ ባንክ ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ሀብታሙ ታዬ እንደነገሩን ጅማ ላይ ተጨማሪ የዓይን ባንክ ለመክፈት የተጀመሩት ስራዎች ተጠናቀው ባንኩ ስራ እንዲጀምር ተደርጓል ብለዋል፡፡
Comments