ግንቦት 13/2018
መጪው ክረምት በኤልኒኖ ምክንያት ሊከሰት ይችላል የተባለውን የድርቅ ስጋት የሚመለከታቸው ተቋማት ለገበሬው እና ሌላም ጉዳዩ ለሚያገባቸው መረጃውን እንዲያደርሱ ማሳሰቢያ ተሰጥቷቸዋል፡፡
መረጃውን ከማድረስ ባሻገር አስፈላጊው ቅድመ ጥንቃቄ ሳያደርጉ ቀርተው ጉዳት ከተከሰተ ተጠያቂ የሚሆኑበት አሰራር መዘርጋቱን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (IGAD) ተናግሯል፡፡
የዘንድሮው የክረምት ዝናብ ጥሩ አጀማመር ቢኖረውም በነሃሴ እና መስከረም ወራቶች ግን ደረቅ ሰሞናት ሊበዙ ፤
የዝናብ መዋዠቅ እና መቆራረጥም ሊታይ እንደሚችል የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሊጂ ኢንስቲትዩት ከሠሞኑ ይፋ ባደረገው ትንበያው ማሳወቁ ይታወሳል።
Comments