መድሀኒቶችና የህክምና ቁሳቁሶች ከግምጃ ቤት ጀምሮ እስከ ስርጭት ድረስ ከፍተኛ ቁጥጥር እንዲደረግበት የሚያስችል የዲጅታል ሥርዓት ሊዘረጋ መሆኑ ተሰማ
TRACK

መድሀኒቶችና የህክምና ቁሳቁሶች ከግምጃ ቤት ጀምሮ እስከ ስርጭት ድረስ ከፍተኛ ቁጥጥር እንዲደረግበት የሚያስችል የዲጅታል ሥርዓት ሊዘረጋ መሆኑ ተሰማ

Avatar

መስከረም 9 2018

መድሀኒቶችና የህክምና ቁሳቁሶች ከግምጃ ቤት ጀምሮ እስከ ስርጭት ድረስ ከፍተኛ ቁጥጥር እንዲደረግበት የሚያስችል የዲጅታል ሥርዓት ሊዘረጋ መሆኑ ተሰማ።

በኢትዮጵያ በሁሉም ክፍሎች መድኃኒቶችንና የህክምና ቁሳቁሶችን የመግዛት፤ የማከማቸት እና የማከፋፈል ኃላፊነት የተሰጠው የኢትዮጵያ የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ይህ መንገድ የስራዬን ትክክለኝነት ያረጋግጥልኛል ብሏል።

በኢትዮጵያ የመድኃኒት ቁጥጥር እንዲሻሻል እና ከፍተኛ ሐብት የወጣበት ሐብት ቆጠራ ሥርዓት ትክክለኛነት እንዲረጋገጥ ይህ የዲጂታል መንገድ እንደሚያግዝ የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ ስማርት የዲጂታል ጤና አቅርቦትና ሰንሰለት ለመዘርጋት ኢትዮ ቴሌኮምና የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ውል ማሰራቸውን ሰምተናል።

Comments

Avatar