ግንቦት 10/2018
የኢትዮጵያ ነጋዴዎች ከአንድ እቃ ላይ የሚያተርፉት ምን ያክል ነው?
የተለያዩ ሀገሮች በገበያው ያልተገባ የንግድ ሥርዓት እንዳይኖር የትርፍ ጣራ ወይንም የትርፍ ህዳግን በህግ ይወስናሉ።
በኢትዮጵያ ይህ ሥርዓት ባለመኖሩ ገበያው የሚመራው በዘፈቀደ እንዲሆን አድርጎታል ይባላል።
በቅርቡ በነዳጅ እጥረት ምክንያት የተፈጠረው ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ የነዳጅ ችግሩ ሲፈታ ወደነበረበት ይመለሳል ወይ?
የሚል የስጋት ጥያቄን ሸማቹ ሲያነሳ ይሰማል። ይህ ጥያቄም የሚነሳው የመቆጣጠሪያ መንገዱን ከመጠራጠር ነው ይባላል።
ለመሆኑ በገበያው በየጊዜው የሚታየውን የዋጋ መለዋወጥ ለመቆጣጠር ምን ቢደረግ ይበጃል? ባለሙያዎችን አነጋግረናል፡፡
ዘገባውን ለማድመጥ….
ማርታ በቀለ
Comments