TRACK
ልዩ መለያ ወይም ‘’ባር ኮድ’’ የሌላቸው ነባር ደረሰኞች ከፊታችን ጥር ወር በኋላ ሙሉ ለሙሉ ከአገልግሎት ውጪ እንደሚሆኑ የገቢዎች ሚኒስቴር ተናገረ፡፡
ታህሳስ 21/2018
ልዩ መለያ ወይም ‘’ባር ኮድ’’ የሌላቸው ነባር ደረሰኞች ከፊታችን ጥር ወር በኋላ ሙሉ ለሙሉ ከአገልግሎት ውጪ እንደሚሆኑ የገቢዎች ሚኒስቴር ተናገረ፡፡
ከካሽ ሬጅስተር የሚወጡ ደረሰኞችንም ወደ ኤሌክትሮኒክ መላ ለመቀየር ስራ ተጀምሯል ብሏል።
ከደረሰኝ መስጠት እና መቀበል ጋር የተገናኙ ሰፋ ያሉ ችግሮች እንደሚታዩ የገቢዎች ሚኒስቴር ተናግሯል።
ሃሰተኛ ደረሰኝ ለመንግስት ማቅረብ ፤በታክስ ከፋዮች ስም ሃሰተኛ ደረሰኝ ማዘጋጀትና ያልተከፈለ የመንግስት ዕዳ አለብህ በማለት ፤ ሰዎች ላይ ያልተገባ ጫና መፍጠር ከችግሮቹ መካከል እንደሆኑ በሚኒስቴሩ የታክስ ማጭበርበር ምርመራ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሢሣይ ገዙ ጠቅሰዋል።
Comments