TRACK
ከቀናት በፊት በተከበረው የፋሲካ በዓል ወቅት የሸማቾች ህብረት ስራ ማህበራት አንድ ኪሎ ስጋ በ650 ብር እንዲሸጡ ተወስኖ በዚሁ መሰረት ሲያቀርቡ ቆይተዋል።
ሚያዝያ 15/2018
ከቀናት በፊት በተከበረው የፋሲካ በዓል ወቅት የሸማቾች ህብረት ስራ ማህበራት አንድ ኪሎ ስጋ በ650 ብር እንዲሸጡ ተወስኖ በዚሁ መሰረት ሲያቀርቡ ቆይተዋል።
ዋጋው አያዋጣንም ያሉ አንዳንድ የሸማቾች ህብረት ስራ ማህበራት ግን በሱቆቻቸው ስጋ አልነበረም።
ለመሆኑ ማህበራቱ ያለ ትርፍ አንዳንዴም በኪሳራ ምርቶቹን እንዲሸጡ ማድረግ ትክክል ነው ወይ?
የህብረት ስራ ማህበራት የተቋሙበት አላማ ሸማቾች ጥራት ያለው ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ፤ አምራቾችም ለምርታቸው ተገቢው ክፍያ እንዲፈጸምላቸው ማድረግ የሚል ነው።
ብዙዎችም በተለይ የፍጆታ ምርቶችን በእነዚሁ ማህበራት ከተቋቋሙ ሱቁች በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት እንደቻሉ ይናገራሉ።
በሌላ በኩል የሸማች ህብረት ስራ ማህበራት ምርቶችን የሚሸጡበት ዋጋ ገደብ የተቀመጠለት ስለሆነ ሊኪሳራ እየዳረጋቸው ነው የሚሉ ሰዎች አሉ።
ለአብነትም ከቀናት በፊት በተከበረው የፋሲካ በዓል ሠሞን ማህበራቱ አንድ ኪሎ ስጋ ከ650 ብር በላይ እንዳይሸጡ በመወሰኑ ሲቸገሩ እንደነበር ያነሳሉ።
በዚህ ዋጋ ሸጠን ኪሳራ ውስጥ አንገባም ያሉም እንዳሉ ሠምተናል።
Comments