ኢትዮጵያ መጋቢት ወር ላይ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ያጸደቀችው የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ የት ደረሰ?
TRACK

ኢትዮጵያ መጋቢት ወር ላይ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ያጸደቀችው የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ የት ደረሰ?

Avatar

መስከረም 8፣2017

ኢትዮጵያ መጋቢት ወር ላይ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ያጸደቀችው የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ የት ደረሰ?

ወደ ትግበራስ መች ይገባ ይሆን?

የፍትህ ሚኒስቴር አማካሪ ታደሰ ካሣ(ዶ/ር) በዚህ ዓመት ትግበራው ይጀመራል ብለዋል፡፡

የሽግግር ፍትህ ልዩ ዐቃቤ ህግ ልዩ ችሎት የእውነት ምህረት እና ማካካሻ ኮሚሽን እንዲሁም የሁሉም ተቋማት ማቋቋምያ አዋጆች ረቂቅ ተዘጋጅቷል ብለዋል፡፡

ጥቅምት ወር ላይ ሁሉም ረቂቆች እንዲያልቁ በወሩ መጨረሻ ደግሞ በሁሉም ረቂቆች ላይ የህዝብ ውይይት እንዲካሄድ እና ግብረ መልስ እንዲሰበሰብ ታቅዷል ብለዋል ታደሰ ካሣዶ/ር፡፡

በህዳር ወር ደግሞ የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ከሚሰራቸው የመጀመሪያ ስራዎቹ ዋናው የሽግግር ፍትህ ተቋማትን ማቋቋምያ አዋጆችን ማጽደቅ እንዲሆን ነው አቅደን እየሰራን ያለነው ብለዋል፡፡

አሁን ኢትዮጵያ ያለችበት የሰላም ሁኔታ ለሀገራዊ ምክክር እንቅፋት መሆኑን እየተነረ ነው የሽግግር ፍትህ ለመተግበር ምቹ ሁኔታ አለ ውይ? ላልናቸው ጥያቄ፤ ታደሰ ካሣ(ዶ/ር) ‘’ለኔ የሽግግር ፍትህን ለመተግበር ከዚህ የተሻለ ገዜ አለ ብዬ አላስብም’’ ሲሉ መልሰዋል፡፡

‘’በአንዳንድ አካባቢዎች ያለው ግጭት እንቅፋት ሊሆን ይችላል የሽግግር ፍትህ የሚፈልገው አንዱ እና መሰረታዊው ጉዳይ ሰላም ነው’’ ብለዋል አማካሪው፡፡

Comments

Avatar