ግንቦት 12/2018
በታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ግብር ከፋይዮች አንዴ የተወሰነባቸውን ግብር መጠን ተገቢ እንዳልሆነ የሚያስረዳ አዲስ ማስረጃ እንዳያቀርቡ መከልከሉ ከፍተኛ ትችት ከባለሞያዎች ቀረበበት።
የገንዘብ ሚኒስቴር በበኩሉ አዲስ ማስረጃ ማቅረብ ሙሉ በሙሉ አልተከለከልም፣ የሚፈቀድብት ሁኔታ አለ ብሏል፡፡
ረቂቁ በአንድ ግብር ዘመን ከሁለት ጊዜ በላይ ቅጣት የተጣለበት የግብር ከፋይ ድርጅት ስራ አስኪያጅ፣ የፋይናንስ ሀላፊ ጨምሮ ሌሎች ተሳታፊዎችን በወንጀል ህግ እንዲጠየቁ የሚያደርግ ነው።
በረቂቅ አዋጁ ላይ ትችቱ የቀረበው የገንዘብ ሚኒስቴር ግንቦት 11 ቀን 2018 ዓ.ም በዋና መስሪያ ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ውስጥ ባካሄደው የባለድርሻ አካላት ወይይት ላይ ነው።
Comments