TRACK
አካባቢን መበከላቸው ተረጋግጦ የማስተካከያ እርምጃ እንዲወሰዱ በፍርድ ቤት በኩል የሚሰጡ ውሳኔዎችን አንዳንድ ተቋማት ተፈፃሚ እያደረጉ አይደለም ተባለ
ሐምሌ 18 2017
አካባቢን መበከላቸው ተረጋግጦ የማስተካከያ እርምጃ እንዲወሰዱ በፍርድ ቤት በኩል የሚሰጡ ውሳኔዎችን አንዳንድ ተቋማት ተፈፃሚ እያደረጉ አይደለም ተባለ፡፡
አካባቢን በበኩሉ ተቋማት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ በፍርድ ቤት ውሳኔ በሚሰጥባቸው ላይ ስልጣንን ተገን አድርገው ውሳኔው ተፈፃሚ እንዳይሆን እክል የሚፈጥሩ ግለሰቦች እንዳሉም ሰምተናል፡፡
በአካባቢው ብክለት ላይ እየሰራ ያለው ቁም ለአካባቢ የተሰኘው መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ውስጥ በበጎ ፈቃደኛ የህግ ባለሙያዎች ሕዝቡን ወክለው በከወኑት ስራ አካባቢ ይበክሉ የነበሩ 7 የመንግስት ተቋማት ላይ የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ በፍርድ ቤት ውሳኔ ቢሰጥም ተፈፃሚ የሆኑት 4ቱ ብቻ መሆናቸውን የተቋሙ መስራች እና የቦርድ ሰብሳቢ አቶ መልካሙ ኦጎ ነግረውናል፡፡
ቀሪዎቹ ግን መንግስትን በማይወክሉ ነገር ግን በመንግስት ተቋማት ውስጥ ባሉ ግለሰቦች እንቅፋትነት ውሳኔዎቹ ያልተፈፀሙ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
Comments