ህዳር 9 2018
በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ሰብአዊ ድጋፎች ላይ የሚከወኑ ስራዎችን የሚደግፉ ዓለም አቀፍ ተቋማት ተሳትፎ ከጊዜ ወደ ጊዜ የቀነሰ ነው፡፡
በዚህም ሀገሪቱ ፊቷን ሀገር በቀል ወደሆኑና በራስ አቅም ዘላቂ ድጋፍ ወደ ሚገኝበት መንገድ እያዞረች መሆኑ ተነግሯል።
በኢትዮጵያ በተቀናጀ መንገድ የሰብአዊ እርዳታ ለማድረግ የሚያስችል ጥምረት ተመስርቷል።
በተለያዩ የድጋፍ ዘርፎች ላይ የሚሰሩ 20 ሀገር በቀል የእርዳታ ድርጅቶች የመሰረቱት ''the consortium of humanitarian actors for national grow empowerment'' ወይም CHANGE የሚል ስያሜ የተሰጠው ጥምረቱ ዛሬ በስካይላይት ሆቴል ይፋ ሆኗል፡፡
Comments