መስከረም 8፣2017
የኢትዮጵያ ጠለፋ መድን(Ethiopian Reinsurance) አገልግሎት ፍለጋ ከሀገር ውጭ ከሚወጣው ምንዛሪ 50 ሚሊዮን ዶላር አድኛለሁ አለ፡፡
ግለሰቦች እና ደርጅቶች በህይወት፣ በንብረት እና በሌሎች በሚደርሱባቸው አደጋዎች ሽፋን የሚሰጡ የኢንሹራን ኩባንያዎችን ሽፋን ለመስጠት የተቋቋመው የኢትዮጵያ ጠለፋ መድን በስራ ላይ 8 ዓመታት ማስቆጠሩ የተነገረለት ሲሆን በ1 ቢሊዮን ብር የተቋቋመ ድርጅት መሆኑ ተነግሮለታል፡፡
ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ የኢንሹራንስ ኩባንያዎች የመድን አገልግሎት ፍለጋ በተለያዩ ሀገራት በተቋቋሙ ኢንሹራንስ ሰጭ ድርጅቶች ዘንድ ይሄዱ እንደነበር የተናገሩት የኢትዮጵያ ጠለፋ መድን ሥራ አስፈፃሚ አቶ ፍቅሩ ፀጋዬ አገልግሎቱንም የሚያገኙት በውጭ ምንዛሪ ነበር ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ጠለፋ መድን(Ethiopian Reinsurance) ከተቋቋመ በኋላ ግን 50 ሚሊየን ዶላር ማትረፍ ችለናል፤ የተለያዩ ተቋማትም ወደ ድርጅታችን በመምጣት አገልግሎቱን ማግኘት ጀምረዋል ብለዋል አቶ ፍቅሩ፡፡
ከስምንት አመታት በፊት የReinsurance አገልግሎት ፍለጋ 30 በመቶው ገንዘብ ከሀገር ይወጣ እንደነበር የተናገሩ ሲሆን በሌላ በክልል ደግሞ ከ10 የአፍሪካ አገራት ጋር በጋራ በመስራት የውጭ ምንዛሬ እያስገኘን ነው ይላሉ፡፡
67 በመቶ ገደማው በኢንሹራንስ ኩባንያዎች ባለቤቶቹ የተያዘው የኢትዮጵያ ጠለፋ መድን ወይም Ethiopian Reinsurance 31 ከመቶው ደግሞ በሰባት ባንኮች የተቋቋመ መሆኑን ሰምተናል፡፡
Comments