ታህሳስ 16፣2017
ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የፋይናንስ ተቋማት ዳታን ወይም መረጃን ተንትኖ ውሳኔ መስጠት ላይ የእውቀት ክፍተት አለባቸው ተባለ፡፡
አሁንም ድረስ የፋይናንስ ዘርፉ ውሳኔዎችን እየሰጠ ያለው በባለሙያዎችእገዛ ብቻ ነው ተብሏል፡፡
ይህንን ክፍተት ለመሙላት ኤመራልድ ኢንተርናሽናል ኮሌጅና የካፒታል ፋይናንስ ልህቀት ማዕከል በመተባበር ባለሙያ ለማሰለልጠን ተዘጋጅተዋል፡፡
የካፒታል ፋይናንስ ልህቀት ማዕከል የስልጠናና ልማት ዳይሬክተር ሃብታሙ አበባው(ዶ/ር) ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የፋይናንስ ዘርፍ ቴክኖሎጂን ተንተርሶ ዳታ መተንተን ላይ የእውቀት ክፍተት መኖሩን ነግረውናል፡፡
Comments