ሚያዝያ 17 2017
ለኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት የሚያገለግሉ ግብአት አምራቾች በየጊዜው የሚወጣው የዋጋ ትመና ጊዜውን ያገናዘበ አይደለም ሲሉ ተናገሩ፡፡
ይህ የተባለው ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከአምራች ተቋማት ጋር ባደረገው ውይይት ላይ ነው፡፡
ትራስፎርመርን ጨምሮ ሌሎች ግብአቶች ሀገር ውስጥ ለማምረት ጥሬ እቃው የሚመጣው ከውጪ ሀገር ነው የውጪ ምንዛሪ በየጊዜው ዋጋ ይቀያየራል ያሉት አምራቾች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ግዢ ሲፈፅም ይህንን ታሳቢ እያደረገ አይደለም ብለዋል፡፡
በተለይም ለትናስፎርመር እድሳት የሚሰጠው ዋጋ ዝቅተኛ ነው ለአምራቹ አዋጭ አይደለምም ተብሏል፡፡
Comments