የሸጎሌ የቁም እንስሳት ገበያ ከቦታው አንዲነሳ በፍርድ ቤት የመጨረሻ ውሳኔ ተሰጠ
TRACK

የሸጎሌ የቁም እንስሳት ገበያ ከቦታው አንዲነሳ በፍርድ ቤት የመጨረሻ ውሳኔ ተሰጠ

Avatar

ሐምሌ 3፣ 2016

የሸጎሌ የቁም እንስሳት ገበያ ከቦታው አንዲነሳ በፍርድ ቤት የመጨረሻ ውሳኔ ተሰጠ፡፡

በመኖሪያ መንደር አካባቢ የተገነባውና በሚፈጥረው የአካባቢ ብክለት ነዋሪዎች ሲያማርሩበት የቆየው የገበያ ማዕከሉ ከዚህ ቀደምም ከቦታው እንዲነሳ በተከማዋ #ፍርድ_ቤት ጉለሌ ምድብ ችሎት ተወስኖበት ነበር፡፡፡

ተከሳሾች የጉለሌ ክፍለ ከተማ ንግድ ፅ/ቤት እና የኢትዮጵያ የቁም እንስሳት ነጋዴዎች ማህበር ይግባኝ ብለው ሲከራከሩ ቆይተዋል፡፡

የአካባቢውን ህዝብ ወክሎ ቁም ለአካባቢ የተሰኘው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅትም ለአምስት ዓመት በፍርድ ቤት ሞግቶ የመጨረሻ ውሳኔ ከትናንት በስትያ ተሰጥቷል፡፡

ገበያው #የአካባቢ_ብክለት ስለመፍጠር አለመፍጠሩ በገለልተኝነት ማስረጃ እንዲያቀርብ የተጠየቀው የፌዴራሉ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ብክለት ስለመኖሩ በማረጋገጡ ፍርድ ቤቱ ገበያው ከቦታው እንዲነሳ የመጨረሻ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡

ትዕግስት ዘሪሁን

Comments

Avatar