ነሐሴ 7፣2016
ከገንዘብ ንክኪ ነፃ የሆነ እና የክፍያ ስርአትን ለማዘመን የሚሰራው ሳንቲም ፔይ ፋይናንሺያል ሶሉሽን አ.ማ በመጪው ዓመት ከ10,000 በላይ ፖስ ማሽኖችን ለማሰራጨት አቅጄ እየሰራሁ ነው አለ፡፡
በተለያዩ የመገበያያ ቦታዎች ክፍያዎችን በዲጂታል እንዲከወኑ የሚያግዙ ወይም ለግብይት የሚያገለግሉ ፖስ ማሽኖችን በ2017 በጀት ዓመት ከ10,000 በላይ የሚሆኑ ማሽኖችን ለማሰራጨት ተዘጋጅቻለሁ ብሏል፡፡
ድርጅቱ ወደ ስራ ከገባ ጀምሮ ከ1000 ማሽኖች በላይ አከፋፍሎ ስራዎችን ሲከውን መቆየቱን ሰምተናል፡፡
ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘርፉ በበቂ ሁኔታ አለመበርታ ተደጋግሞ የሚነሳ ጉዳይ ቢሆንም ሳንቲም ፔይ ፋይናንሺያል ሶሉሽን ወደ ስራ ያስገባውን ከገንዘብ ንክኪ ነፃ የሆነ የክፍያ ስርአትን ላይ ግን ተጠቃሚው ከፍተኛ ነው ይላሉ የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ትንሳኤ ደሳለኝ፡፡
Comments