ጥር 13/2018
አለም አቀፍ ገዥዎች በዋጋ ምክንያት ለኢትዮጵያ ሰሊጥ የሚያሳዩትን ፍላጎት እየቀነሱ ነው ተባለ።
የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት እና ብራዚል ሰሊጥን ከኢትዮጵያ ባነሰ ዋጋ ለአለም ገበያ እያቀረቡ በመሆናቸው የገዥዎች ፍላጎት ወደ እነሱ እያደላ ስለመሆኑ ተነግሯል።
ሰሊጥ ከሀገር ውስጥ አምራቾች የሚገዛበት ዋጋ ከፍ ያለ በመሆኑ በአለም አቀፍ ግብይቱ ላይ ተፅዕኖ እየፈጠረ እንደሚገኝ ተነግሯል።
ከአምራቾች ከፍ ባለ ዋጋ የተገዛውን ሰሊጥ ተወዳዳሪ ሆኖ በአለም ገበያ ላይ መሸጥ እንዳልተቻለ ከኢትዮጵያ ጥራጥሬ፣ ቅባት እህሎችና ቅመማ ቅመም ላኪዎች ማህበር ሠምተናል።
Comments