በትግራይ ክልል የግሪሳ ወፍ መንጋ በሰብል ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ነው ተባለ
TRACK

በትግራይ ክልል የግሪሳ ወፍ መንጋ በሰብል ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ነው ተባለ

Avatar

ህዳር 25፣2017

በትግራይ ክልል የግሪሳ ወፍ መንጋ በሰብል ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ነው ተባለ፡፡

በትግራይ ደቡባዊ ዞን በ650 ሄክታር የማሽላ ሰብል ላይ የተከሰተው #የግሪሳ_ወፍ መንጋ እስካሁን 320 ሄክታር የማሽላ ሰብልን ሙሉ በሙሉ ማውደሙን ተነግሯል፡፡

ይህንን ለሸገር ራዲዮ የተናገሩት የክልሉ የአደጋ ስጋት ቅድመ ማስጠንቀቂያ መረጃ ትንተና ኃላፊው አቶ ገብረአብ ገ/መድን ናቸው፡፡

የወፍ መንጋው ወደ ቆላማው የማሽላ አምራች #የትግራይ_ወረዳዎችም እየተስፋፋ ነው ተብሏል፡፡

Comments

Avatar