ሰኔ 12 2017
124 የመንግስት አገልግሎቶች በአንድ ማዕከል እየተሰጡ መሆኑን የሲቨል ሰርቪስ ኮሚሽን ተናገረ።
በአገልግሎት አሰጣጣቸው ተደጋግሞ በማህበረሰቡ ቅሬታ የሚነሳባቸው የመንግስት አገልግሎቶችን፤ ለአገልግሎት አሰጣጥ የተመቹና ቀልጣፋ አገልግሎት የሚሰጥባቸው እንዲሆኑ ለማድረግ ስራዎች መጀመሩን ኮሚሽኑ ተናግሯል።
በዚህም ከወንኩት ባለው ሪፎርም የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሚል የ23 የመንግስት ተቋማትን 124 አገልግሎቶች ቀልጣፋ አገልግሎቶች እንዲሰጥባቸው ለማስቻል ወደ አንድ ማዕከል ገብተዋል ብሏል።
ከ124ቱ አገልግሎች መካከል የፓስፖርት አገልግሎት፣ የዲጂታል መታወቂያ፣ የሰነዶች ማረጋገጫና የንግድ ፍቃድ አገልግሎቶች እንደሚገኙበት ከኮሚሽኑ ሰምተናል።
ይህ የተባለው ከፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 14 እስከ ሰኞ ሰኔ 16 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ አዲስ አበባ በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ የምታስተናግደውን አለም አቀፍ ጉባኤ አስመልክቶ በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን መግለጫ በተሰጠበት ወቅት ነው።
ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫውን የሰጡት የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መኩሪያ ሃይሌ(ዶ/ር) በጉባኤው ኢትዮጵያ አገልግሎቶችን ለማዘመን የሰራችውን ስራ አስመልክቶ ተሞክሮዎቿን ታቀርባለች ብለዋል።
ለ3 ቀናት በትዩ የሚካሄደው ጉባኤ የመጀመሪያው የአፍሪካ ህብረት አባላት ሀገራት የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳድር 10ኛ ጉባዔ ሲሆን ሁለተኛው በተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ቀጣናዊ ፎረም መሆኑ ተጠቅሷል፡፡
Comments