TRACK
ከሚወለዱ 10,000 ህፃናት ውስጥ 80 የሚሆኑት የነርቭ ዘንግ ክፍተትና የጭንቅላት ውስጥ ውሃ መቋጠር ወይም ሀይድሮሴፋለስ ችግር ያጋጥማቸዋል ተባለ፡፡
ጥር 28/2018
በኢትዮጵያ ከሚወለዱ 10,000 ህፃናት ውስጥ 80 የሚሆኑት የነርቭ ዘንግ ክፍተትና የጭንቅላት ውስጥ ውሃ መቋጠር ወይም ሀይድሮሴፋለስ ችግር ያጋጥማቸዋል ተባለ፡፡
ችግሩ በሀገሪቱ የሚገባውን ያህል ትኩረት ያልተሰጠው በመሆኑ በማህበረሰብ ላይ የሚያደርሰው ጫና ከፍተኛ ነው ተብሏል፡፡
በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊንየም የህክምና ኮሌጅ የህጻናት የነርቭ ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት ሐኪም የሆኑት ዶክተር ሱራፌል መኮንን ስለ ህመሞቹ ይህንን ያስረዳሉ፡፡
ስፓይና ቢፊዳ ( #Spina_Bifida ) ማለት ከነርቨ ዘንግ የአፈጣጠር ችግሮች ውስጥ አንዱ ሲሆን የአከርካሪ አጥንትና የህብለሰረሰር በአግባቡ አለመዘጋት (ክፍተት) ነው።
በአብዛኛው ጊዜ ስፓይና በፊዳ ያለባቸው ሕጻናት ፈሳሽ በአጎላቸው ወስጥ ስለሚከማች ሃይደሮ ሴፋለስም ያጋጥማቸዋል።
Comments