ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት የተደረጉ ለውጦች የታሰበላቸው አላማ አላሳኩም ተባለ፡፡
TRACK

ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት የተደረጉ ለውጦች የታሰበላቸው አላማ አላሳኩም ተባለ፡፡

Avatar

ታህሳስ 15/2018

ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት የተደረጉ ለውጦች የታሰበላቸው አላማ አላሳኩም ተባለ፡፡

ይህ የተባለው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዲጂታል ቴክኖሎጂ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አተገባበር ዙሪያ በተደረገ ውይይት ነው፡፡

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቋንቋና ትምህርት ኮሌጅ ባልደረባ የሆኑት በላይ ተፈራ(ፕ/ር) በዚህ ዙሪያ የመወያያ ሀሳብ አቅርበዋል፡፡

75 ዓመታት ባስቆጠረው የኢትዮጵ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ታሪክ ውስጥ በርካታ ለውጦች ቢደረጉም ያሰቡት ግብ ማሳካት አልቻሉም ብለዋል፡፡

ለዚህ ብዙ ምክንያቶች ቢኖሩም ዋነኞች ተብለው ከሚጠቀሱት መካከል ለውጦች ሲደረጉ ከታች እስከላይ ያለው አመራር በትክክል ተረድቶ አይሰራውም፣ ወዲያው የመጣው ለውጥ ውይይት ሳይደረግበት በጥናት ሳይደገፍ ይተገበራል ይላሉ፡፡

ከ75 ዓመት በፊት ሲጠየቅ የነበረው ጥያቄ የኢትዮጵ ከፍተኛ ትምህርት ሀገርኛ አይደሉም የሚል ነበር አሁንም ድረስ ይህ ጥያቄ አለ ሲሉም ያብራራሉ፡፡

በላይ ተፈራ(ፕ/ር) ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለውጥ ሲያደርጉ አካባቢውን በተገቢው መንገድ ማየት አለባቸው ሲሉም ነግረውናል፡፡

Comments

Avatar