መጋቢት 25/2018
የመካከለኛ ምስራቅ ጦርነት ያስከተለው የነዳጅ እጥረት አምራች ፋብሪካዎች ላይም ተፅዕኖ እያሳደረ ነው፡፡
የተለያዩ ምርቶችን ለገበያ የሚያቀርቡ ፋብሪካዎች በነዳጅ እጥረት ምክንያት ጥሬ እቃ ተወዶብናል ፣ ተፅዕኖዎቹን ተቋቁመን የምርት ሂደቱ እንዳይስተጓጎል ጥረት እያደረግን ነው ብለዋል፡፡
በመካከለኛው ምስራቅ ኢራን ከአሜሪካና እስራኤል ጋር እያካሄደችው ያለው ጦርነት በእኛም ሀገር እንቅስቃሴዎች ላይ ተፅዕኖውን እያሳረፈ ነው።
የትራንስፖርት ዘርፉ ተጠቃሽ ሲሆን አሁን ያለውን ሁኔታ ታሳቢ ያደረገ የነዳጅ ግብይት መከተል እንደሚገባ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከሠሞኑ ማሳሰቡ ይታወሳል።
Comments