''የመንገድ መሰረተ ልማቶች አካል ጉዳተኞችን አገናዝበው የሚገነቡ ባለመሆናቸው፤ ለከፍተኛ የትራፊክ አደጋ እንዲሁም የአካል ጉዳት እየዳረጋቸው ነው''
TRACK

''የመንገድ መሰረተ ልማቶች አካል ጉዳተኞችን አገናዝበው የሚገነቡ ባለመሆናቸው፤ ለከፍተኛ የትራፊክ አደጋ እንዲሁም የአካል ጉዳት እየዳረጋቸው ነው''

Avatar

ሰኔ 26 2017

በአዲስ አበባ የሚሰሩ አብዛኛዎቹ የመንገድ መሰረተ ልማቶች አካል ጉዳተኞችን አገናዝበው የሚገነቡ ባለመሆናቸው፤ ለከፍተኛ የትራፊክ አደጋ እንዲሁም የአካል ጉዳት እየዳረጋቸው ነው ተባለ፡፡

በተለይ የዚህ ጉዳት ሰለባ የሚሆኑት አብዛኛዎቹ አይነስውራን መሆናቸውንና በትራፊክ አደጋ ምክንያትም ብዙዎቹ ህይወታቸውን እያጡ እንደሆነ ተነግሯል፡፡

በመንገዶች ያለመመቸት በአሽከርካሪዎች ለአካል ጉዳተኞች ቅድሚያ ሰጥቶ አለማሽከርከርና በሌሎችም ምክንያቶች ብዙ አካል ጉዳተኞች ለከፍተኛ የትራፊክ አደጋና ሞት ተዳርገዋል ተብሏል፡፡

በዚህ ምክንያት ከቤት በሰላም ወጥቶ ያሰቡት ለመድረስ በተለይ አይነስውራን ትልቅ ስጋት ሆኖባቸዋል፣ የጉዳት ሰለባም እየሆኑ ነው ሲል የኢትዮጵያ አይነስውራን ብሔራዊ ማህበር ተናግሯል፡፡

የማህበሩ የስራ አመራር ቦርድ ፕሬዝዳንት አቶ አበራ ረታ ባለፉት ሁለት ዓመታት በመንገድ ላይ በደረሰ የትራፊክ አደጋ ጉዳት የገጠማቸውና ለሞት የተደረጉ ዓይነ ስውራን በርካታ ናቸው ብለዋል፡፡

በመንገድ ላይ ያለው ሁኔታ ተደራሽ ካለመሆኑ አንፃር አንዳንድ አገራት ውስጥ ዓይነ ስውራን መንገድ በሚያቋርጡበት ሰዓት አንድም እነሱን ተመልክቶ መብራት የሚያበራ የደህንነት ካሜራ ይገጠማል ስለዚህ ካሜራው ለይቶ በራሱ በሚያበራው የትራፊክ መብራት በእንቅስቃሴ ላይ ያለ አሽከርካሪ እንዲቆም ስለሚያደርግ ከአደጋ የሚጠብቅ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ነው ይህንን ወይም ተመሳሳይ ሌሎች መላዎች በኢትዮጵያ ቢኖሩ አደጋውን መቀነስ እንደሚቻል ተናግረዋል፡፡

Comments

Avatar
litha melamane

awesome. greetings from cape town

There is no more content to load