ታህሳስ 21/2018
ግብርናው ዘርፍ የብድር አቅርቦት ከማያገኙ ዘርፎች መካከል ቀዳሚው ነው ተባለ፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ ግብርናው የብድር አቅርቦት ከፋይናንስ ተቋማት እንዳያገኝ ከሚያደርጉት ምክንያቶች ዋነኛው በዝናብ ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ነው ይላሉ ያነጋገርናቸው የግብርና ኦኮኖሚ ባለሙያ፡፡
በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የግብርና ኢኮኖሚስት ምርምር ዳይሬክተር እና ተመራማሪ ታደለ ማሞ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚቀርበው ብድር ውስጥ ግብርናው የሚያገኘው 10 በመቶ ብቻ ነው፡፡
ከ10 በመቶ ብድሩ መካከል አብዛኛው ብድር በግብርና ምርት ማቀነባበር ስራ ለተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች የሚቀርብ ነው ተብሏል፡፡ ገበሬው አሁንም ብድር እያገኘ አይደለም ብለዋል፡፡
Comments