‘’የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ድርሻ እጅ ማውጣት ብቻ እየሆነ ነው ወይ?’’ የምክር ቤት አባል
TRACK

‘’የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ድርሻ እጅ ማውጣት ብቻ እየሆነ ነው ወይ?’’ የምክር ቤት አባል

Avatar

ሐምሌ 25፣2016

‘’የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ድርሻ እጅ ማውጣት ብቻ እየሆነ ነው ወይ?’’ ሲሉ አንድ የምክር ቤት አባል ጠየቁ፡፡

አበባው ደሳለው የተባሉ የምክር ቤት አባል ይህን ጥያቄ የጠየቁት ምክር ቤቱ ትናንት ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ ኢትዮጵያ ከአለም አቀፉ የልማት ማህበር የተበደረችውን የ40 ቢሊዮን ብር ብድር እና የ80 ቢሊዮን ብር ወይም የአንድ የአሜሪካ ቢሊዮን ዶላር የድጋፍ ስምምነቱን ለማጽደቅ ምክር ቤቱ በጠራው አስቸኳይ ስበሰባ ላይ ነው፡፡

ሰሞኑን ኢትዮጵያ ያደረገቸው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሽያ እና እሱን ለመደገፍ ይረዳል ያለችውን ብድር ለማግኘት የወሰነችው የውጭ ምንዛሬ ተመን በገበያ መር እንዲሆን ማድረጉ በምክር ቤቱ አባላት የህጋዊት ጥያቄ ተነስቶበታል፡፡

የምክር ቤት አባሉ ‘’የገንዘብ እና ብሄራዊ ባንክ አስተዳደር የውጭ ምንዛሬ ልውውጥን በተመለከተ ምክር ቤቱ ዝርዝር ህግ እንደሚያወጣ ህጉ ያስረዳል ነገር ግን ከዚህ በፊትም በነበረው አሁንም እየሆነ ያለውም ህግ አስፈጻሚው ነው ህግ እያወጣ ያለው የህዝብ ተወካዮች ድርሻ ምንድነው ነው’’ ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

Comments

Avatar