የደረጃ ’’ሀ’’ እና ’’ለ’’ግብር ከፋዮች ግብራቸውን ሲያሳውቁ የሂሳብ መዝገብ እንዲያቀርቡ ሊገደዱ ነው
TRACK

የደረጃ ’’ሀ’’ እና ’’ለ’’ግብር ከፋዮች ግብራቸውን ሲያሳውቁ የሂሳብ መዝገብ እንዲያቀርቡ ሊገደዱ ነው

Avatar

ሚያዝያ 29 2017

የደረጃ ’’ሀ’’ እና ’’ለ’’ግብር ከፋዮች ግብራቸውን ሲያሳውቁ የሂሳብ መዝገብ እንዲያቀርቡ ሊገደዱ ነው፡፡

የተደራጀ የሂሳብ መዝገብ እንዲያቀርቡ በህግ ቢገደዱም 55,000 ግብር ከፋዮች ምንም አይነት የሂሳብ መዝገብ እያቀረቡልኝ አይደለም ሲል የከተማዋ ገቢዎች ቢሮ ተናገረ፡፡

ስለሆነም ቢሮው ከዚህ በኋላ አልታገሳቸውም፤ ከሃምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የደረጃ ’’ሀ’’ እና ’’ለ’’ግብር ከፋዮች ያለ ሂሳብ መዝገብ አይስተናገዱም ብሏል፡፡

ከጥቂቶቹ በስተቀር አብዛኛው ግብር የሚከፈለው በቁርጥ ነበር፤ ከዚህ በኋላ ግን ወደ ማስገደድ እንሸጋገራለን ያሉን የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ናቸው፡፡

Comments

Avatar