መጋቢት 29 2017
የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር ከመሀል ሀገር ጀምሮ ሀዲዱ እስከተነጠፈበት ጅቡቲ ድረስ ፍጥነቴን ልጨምር መሆኑን እወቁት አለ።
ምድር ባቡሩ በሰአት 80 ኪሎ ሜትር መወርወሬ አይቀርም ብሏል።
በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ውስጥ 50 በመቶውን ገቢና ወጪ እቃ በዚሁ መስመር አቀላጥፈዋለሁ ያለው ምድር ባቡር ለዚህም ፍጥነቴን በሰአት 80 ኪሎ ሜትር አደርጋለሁ ብሏል።
በተደጋጋሚ በእንስሳት ግጭት እና ካሳ ሰበብ ጭነት የያዙ ባቡሮች እየታገቱ መቆየታቸው ምድር ባበቡሩን ሲፈትነው ቆይቷል።
Comments