ነሐሴ 24፣2016
በሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ በአብና ቀበሌ ልዩ ስሙ ኞላ በተባለ ቦታ በደረሰው የመሬት መንሸራተት ከቀያቸው የተፈናቀሉ ሰዎች እስካሁን ምንም ዓይነት የአስቸኳይ የእለት ድጋፍ አላገኙም ተባለ።
በመሬት መንሸራተት ሳቢያ የተፈናቀሉ የቤተሰብ አባላት ቁጥር 2,400 መሆናቸውንም ሰምተናል።
የጠለምት ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ወርቅነህ ‘’በወረዳው በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ የአካባቢውን ነዋሪዎች ወደ ሌላ ቀዬ እንዲሰፍሩ ቢደረግም አደጋው ከተከሰተበት ነሀሴ 16 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን ምንም ዓይነት ድጋፍ አላገኙም’’ ብለዋል።
Comments