ሐምሌ 25፣2016
ለመንግስት የጤና ተቋማት በነፃ ለታካሚዎች የሚቀርቡ እንደ ወባ ያሉ መድሃኒቶችን ከሆስፒታሎች በማውጣት በግል ፋርማሲዎች ዋጋ በመጨመር የሚያቀርቡት ላይ ቁጥጥር እየተደረገ ነው ተባለ፡፡
ወባ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ላይ በቂ የመድሃኒት ስርጭት ተደርጓል መድሃኒቱም በነፃ እየተሰጠ እንደሆነ ተነግሯል፤ነገር ግን ለመንግስት የህክምና ተቋማት የሚቀርቡ መድኃኒቶችን ከዛ እያወጡ በግል የመድኃኒት መደብሮች ላይ ዋጋ በመጨመር የሚሸጡ አሉ ተብሏል፡፡
በመንግስት እንዲሁም ከለጋሽ ድርጅቶች ከሚቀርቡ መድኃኒቶች ለወባ ህክምና የሚውለው አንዱ ቢሆንም መድኃኒቱ ከጤና ተቋማት ውጪ በግል ፋርማሲዎች በብዙ ዋጋ እየተሸጠ በመሆኑ ቅሬታ አስነስቷል፡፡
Comments