ታህሳስ 24፣2017
በኢትዮጵያ የሚገኙ ባንኮች ከቀናት በኋላ በነባሩም ሆነ አዳዲስ ውለታ የሚገቡትን ተበዳሪዎች የብድር ወለድ ምጣኔን ከ3 እስከ 5 በመቶ ከፍ ሊያደርጉ በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ሸገር ሬዲዮ ከታማኝ የባንክ ምንጮቹ ሰምቷል፡፡
ይህም የብድር የወለድ ምጣኔው እስከ 20 እና 22 በመቶ ይደርሳል እንደማለት ነው፡፡
ከዓመታት በፊት የነበረውን የገንዘብ የመግዛት አቅም እና የኢኮኖሚውን ሁኔታ እንዲሁም የገቢ መጠናቸውን ታሳቢ በማድረግ ከባንክ በመበደር ከውጭ እቃ የሚያስመጡ ነጋዴዎች ሆኑ ቤት የገዙ ተበዳሪዎች በተበደሩት ወለድ ላይ ከ3 እስከ 5 በመቶ ጭማሪ ይጠብቃቸዋል ተብሏል፡፡
Comments