ሐምሌ 4፣ 2016
ተፈጥሯዊ እና ሠው ሰራሽ በሆኑ ምክንያቶች ዕርዳታ የሚፈልጉ ሰዎችን ቁጥር አጋነው የሚያቀርቡ እና ዕርዳታን ለማይገባቸው ሰዎች የሚያከፋፍሉ ግለሰቦችን ተጠያቂ የሚያደርግ ህግ እየተዘጋጀ ነው ተባለ።
ተፈጥሯዊ እና ሠው ሰራሽ በሆኑ ምክንያቶች ዕርዳታ ለሚፈልጉ ሰዎች በሚቀርብ ድጋፍ ላይ ከሚገጥሙ ችግሮች አንዱ፤ የቁጥር መጋነን እንደሆነ የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ይናገራል።
በተለይ ከኮሚሽኑ ድጋፍ የሚፈልጉ ክልሎች የተረጂዎችን ቁጥር እያጋነኑ እንደሚያቀርቡ ኮሚሽኑ ከዚህ በፊት ነግሮናል።
የተላከን ዕርዳታ ለማይገባቸው ሰዎች የሚያከፋፍሉ እና ለግል ጥቅማቸው የሚያውሉ ግለሰቦች እንደሚገጥሙም ያነሳል።
Comments