ነሐሴ 22፣2016
በባህላዊ ህክምና የሚደረጉ የአጥንት እና መገጣጠሚያ ህክምናዎች በርካቶችን ለሞት እና ለከፋ አካል ጉዳት እየዳረጋቸው መሆኑን ጥናት አሳየ።
ጥናቱን ያካሄደው በኢትዮጵያ የአጥንት ህክምናና የአደጋዎች ህክምና ስፔሻሊስቶች ብሔራዊ ማህበር ውስጥ ‘’BOSAD’’ የተሰኘው የባለሞያዎች የጥናት ቡድን ነው።
ጥናቱም በ6 ክልሎች የተካሄደ ሲሆን በ8 የተለያዩ የህክምና ተቋማት ላይ ያተኮረ መሆኑንም ሰምተናል።
በተለይ በልጆች ላይ የሚስተዋሉ የመውደቅ አደጋ የዚሁ ችግር ሰለባ መሆናቸውም በጥናቱ ተመላክቷል።
Comments