ሐምሌ 18 2017
ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም የህክምና ኮሌጅ ነፃ ዓመታዊ ሙሉ የጤና ምርመራ ማሰናዳቱ ተነገረ፡፡
የትኛውንም ምርመራ በነፃ ታገኛላችሁ ብሏችኋል ሆስፒታሉ፡፡
ሆስፒታሉ ከሐምሌ 21 እስከ 27 2017 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ነፃ የጤና ሙሉ ምርመራ እና ምክር አገልግሎት ማዘጋጀቱን ተናግሯል፡፡
ምርመራው በላቡራቶሪ እና በሌሎች የህክምና መሳሪዎች በመታገዝ ነው አጠቃላይ ነፃ ምርመራ የሚሰጠው መሆኑን፡፡
በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም የህክምና ኮሌጅ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ነዋይ ፀጋዬ ነግረውናል፡፡
Comments