በዓመት ከ7,000 በላይ ሰዎች በኤችአይቪ የሚያዙ ሲሆን አስር ሺህ የሚሆኑ ደግሞ ይሞታሉ
TRACK

በዓመት ከ7,000 በላይ ሰዎች በኤችአይቪ የሚያዙ ሲሆን አስር ሺህ የሚሆኑ ደግሞ ይሞታሉ

Avatar

ግንቦት 11 2017

በዓመት ከ7,000 በላይ ሰዎች በኤችአይቪ ኤድስ #HIV_AIDS የሚያዙ ሲሆን አስር ሺህ የሚሆኑ ደግሞ ይሞታሉ የተባለ፡፡

የስርጭት ምጣኔው ከፍተኛ ሆኖ የታየው በቀን ሰራተኞች በተማሪዎች እና በአጠቃላይ በማህበረሰብ ውስጥ እንዲሆንም ተነግሯል፡፡

እንደ ሀገር የስርጭት መጠኑ ከአንድ በመቶ በታች ነው ሲባል ዝቅተኛ ቢመስልም አሁን ባለበት ካልተገታ በድጋሜ ወረርሽኝ የሚባለው በደረጃ ሊደርስ ይችላል ሲሉ በጤና ሚኒስቴር የኤችአይቪኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ስራ አስፈጻሚ አቶ ፍቃዱ ያደታ ተናግረዋል፡፡

በተለይም ደግሞ ወጣቱ ትውልድ ለበሽታ የሚሰጠው ትኩረት ዝቅተኛ እየሆነ መምጣቱ ወረርሽኝ የመሆን እድሉን ሊያሰፋው ይችላል ሲሉ ስራ አስፈፃሚው አስረድተዋል፡፡

በዚህም ከስድስት መቶ ሺህ በላይ ሰዎች ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ እንዳለ እንደሚገመትም ተናግረዋል፡፡

Comments

Avatar