ሚያዝያ 14 2017
በአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮና በኦዲተርና የሂሳብ ባለሞያዎች ማህበራት መካከል የተፈጠረው ውዝግብ አሁንም አልረገበም፡፡
ውጥረቱን ለማርገብ በማህበራቱ ለቀረበው የእንወያይ ጥያቄ ቢሮው ምላሽ እንደሰጠ ነግሮናል፡፡
የገቢ አሰባሳቢ ቢሮው ለውይይት ለመቀመጥ የማህበራቱን ህጋዊ እውቅና የሚመለከት ማስረጃ እንዲሁም የአባላቱን ዝርዝር በህጋዊ መንገድ አረጋግጣችሁ አምጡ የሚል ቅድመ ሁኔታ ማስቀመጡን አቶ ሰውነት አስረድተዋል፡፡
ቅድመ ሁኔታውን አሟልተው ይመጣሉ ብለን እየጠበቅናቸው ነውም ብለዋል፡፡
ማህበራቱ በበኩላቸው ለቢሮው በደብዳቤ ላቀረብነው የእንወያይ ጥያቄ በደብዳቤ ምላሽ አልሰጠንም፤ይሁንና የተባለውን ቅድመ ሁኔታ እንድናሟላ በስልክ ተነግሮናል፤ በዚህ ጊዜና በዚህ ሰዓት እንወያይ የሚል ቀጠሮ ስላልተሰጠን እሱን እየጠበቅን ነው የሚል ምላሽ የሰጡን ከሶስቱ የኦዲተሮችና የሂሳብ ባለሙያዎች ማህበራት መካከል አንዱ የሆነው የውጭ ኦዲተሮች ማህበር ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ሚሊዮን ማሞ ናቸው፡፡
ማህበራቱ ባሳለፍነው ሳምንት በሰጡት መግለጫ የገቢዎች ቢሮ እንዲያስተባብል የተጠየቀውን ጉዳይ በተመለከተ ምንም የማስተባብለው ነገር የለም ብሏል፡፡
Comments