TRACK
በፊሊፐር ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤት የበቅሎ ቤት ቅርንጫፍ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎችን ወደ 9ኛ ክፍል ሲዛወሩ በሚቀጥለው ዓመት አልቀበልም ማለቱ ቅሬታ ፈጥሯል
ግንቦት 22 2017
በፊሊፐር ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤት የበቅሎ ቤት ቅርንጫፍ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎችን ወደ 9ኛ ክፍል ሲዛወሩ በሚቀጥለው ዓመት አልቀበልም ማለቱ ቅሬታ ፈጥሯል፡፡
ወላጆች የትምህርት ዓመቱ ሊጠናቀቅ ቀናት በቀሩበት በዚህ ጊዜ ተማሪዎቹን በሚቀጥለው ዓመት ተቀብዬ ለማስተማር ቦታ የለኝም የሚል ምክንያት መስጠቱ ሀላፊነት የጎደለው ነው ብለዋል፡፡
እስከ 167 በመቶ የዋጋ ጭማሪ ማድረጉንም ሰምናል፡፡
በሌላ በኩል የትምህርት ጥራትና ቁጥጥር ባለስልጣን በበኩሉ ጉዳዩን ባለሙያ ልኬ እከታተለዋለሁ ብሏል፡፡
Comments