ህዳር 18፣2017
መንግስታዊው የአዲስ አበባ የአካባቢ ጥበቃ ባልስጣን ተቋማት የአካባቢ ብክለት ፈፅመው መሆኑን ወይም አለመሆኑን ለማረጋገጥ ስሄድ ወደ ግቢያቸው እንኳን እንዳልገባ እየተከለከልኩ ነው አለ፡፡
መንግስታዊ ተቋማት ሳይቀር ስራዬን በአግባቡ እንድሰራ እየፈቀዱልኝ አይደለም ብሏል፡፡
የአካባቢ ተፅእኖ ግምገማ ሳይደረግባቸው የንግድ ፈቃድ እና የብቃት ማረጋገጫ የሚሰጡ ተቋማት ስራችንን እያወኩት ነውም ሲል ባለስልጣኑ ተናግሯል።
የአካባቢ ብክለትን ለመከላከል ህጉን ተላልፈው በተገኙት ላይ ባለስልጣኑ የሚወስደውን እርምጃ ባለስልጣኑን የልማት አደናቃፊ አድርገው የሚቆጥሩት አንዳንድ ተቋማት እንዳሉም ተነግሯል።
የባለስልጣኑ የአካባቢ ጥበቃ የህግ ተከባሪነት ዳይሬክተር አቶ ለሜሣ ጉደታ በከተማዋ ውስጥ ያሉ አንዳንድ ኢንዱስትሪዎች አይደለም የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሊደረግባቸው ምን እንደሚያመርቱ እንኳን የማናውቅበት ደረጃ ላይ ደርሰናል ብለዋል።
በቦታው ግምገማ ለማድረግ ሲኬድም ለእኛ በራቸው ዝግ እየሆነ ተቸግረናል ብለዋል፡፡
Comments